


ከእነዚህ የብሔሩ ባህላዊ ሀብቶችና ክዋኔዎች መካከል አንዱ ደግሞ ዛሬ በድምቀት እየተከበረ የሚገኘው የዘመን መለወጫ በዓል የኾነው (ማሽቃሮ) ነው፡፡
ማሽቃሮ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ የብሄረሰቡ ተወላጆች እና ወዳጆች ተስብስበው የነገስታት መናገሻ በኾነውና ከቦንጋ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው “ቦንጌ ሻምበቶ” በጋራ የሚያከብሩት በዓል ነው።
የካፊቾ ብሔር ማሽቃሮ ከመድረሱ አስቀድሞ አዝመራን መሠረት ያደረገ የጊዜ ስሌት ወይም ቆጠራ የሚያደርግ ሲሆን የቀን ቆጠራውም ወርሃ ሐምሌ በገባ በአምስተኛው 77 ብሎ የሚጀምር ሲሆን ይኸም ለማሽቃሮ 77 ቀናት ቀሩት ተብሎ ይወሰዳል።
የአዝመራ ወቅትን መሠረት ያደረገው የቀን ስሌት 77 ቀናት ሲጠናቀቁ መስከረም 12 ወይም 13 ላይ የካፈቾ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል (ማሽቃሮ) ይሆናል ማለት ነው።
በዚህም መሠረት የዘንድሮ ማሽቃሮ በተለያዩ ባህላዊ ክንዋኔዎች ታጅበው የነገስታት መናገሻ “ቦንጌ ሻምበቶ” እየተከበረ ይገኛል።

More Stories
የማሽቃሮን ዕሴት በማዳበር ለልማትና ለህብረ ብሄራዊ አንድነት ግንባታ ማዋል ይገባል – ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
mashiqaaro at bonge shambeto
በ ወብሳይታችhttps://kaffaculturetourism.com ይከታተሉ